Monday, 6 February 2017

የአረንጓዴው ልማት ተስፋዎች




አባ መላኩ
የአገራችን አካባቢዎች በተራሮች ላይ በተሰሩ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ከታች ላሉት ማሳዎች አነስተኛም ሆነ ከፍተኛ ፍሰት ያላቸው ወንዞች ሳይቀሩ ፍሰታቸው የበለጠ እንዲጨምር አድርጓል፤ በድምር ውጤቱም ግድቦችም ከደለል እና አላስፈላጊ ቆሻሾች መሞላት ታድጓል። በአገራችን ከሦስት እና አራት አመታት በፊት የተጎዱ ማሳዎች፣ ቦረቦሮች እና ቁጥቋጦዎችንም ሆነ የግጦሽ ሳር ለመመልከት አዳጋች ነበር። ዛሬ ዛሬ በተሰሩ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች አፈሩም፣ ውሃውም፣ ቁጥቋጦዎችም ከሰውም ሆነ ከእንስሳት ንክኪ ነፃ ተደርገዋል።
ይህ በመሆኑም የደን ልማቱ ተስፋፍቶና የምንጭ ውሃው ጎልብቶ ለማስተዋል ተችሏል። በዚህም አርብቶ አደሩም ሆነ አርሶ አደሩ ዘመን የተሻገረውን የመጠጥ ውሃ ችግርን ለመቅረፍ አስችሎታል። የደን ልማቱ ለአካባቢው ማህበረሰብ እየሰጠ ያለው ጥቅም የላቀ ነው የሚባለው በዋናነት የስራ እድል በመፍጠሩ ነው። የደኑን ጥብቅነት ደጀን በማድረግ ወጣቶች ተደራጅተው በተለያዩ ስራዎች እንዲሰማሩ በማድረግ ስራ አጥ ወጣቶችን የስራ እድል በመፍጠር ሌላ ተልዕኮን እንዲይዝ አድርጓል።
የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት እንቅስቃሴ በተለያዩ አገራትና በዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተቀባይነት እያገኘና ለሌሎች አገራት በአርአያነት እየቀረበ ይገኛል።  ከእነዚህ አገራት መካከልም አሜሪካ አንዷ ናት።
ኢትዮጵያ በጎርጎሮሳዊያኑ 2025 ልታሳካ የምትፈልገውን ከካርቦን ልቀት ነጻ የሆነ ኢኮኖሚ እውን ለማድረግ እየሰራች መሆኗን በበርካቶች ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ ተግባር ሆኗል፡፡ ዴንማርክ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ኖረዌይ፣ ስዊድን እና እንግሊዝ የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ልማት እንደሚደግፉ በተለያየ ወቅት ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡
ባለፉት ዓመታት በፊት የተነደፈውና እስካሁን ድረስ በተገቢው መንገድ እየተከናወነ ያለው  የአየር ንብረት ለውጥንዘላቂ የአረንጓዴ ልማት ለማምጣት በሚያስችል ተግባር ውጤታማ እየሆነ መምጣቱ ያደባባይ ምስጢር ሆኗል።  ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ጥቂት አገሮች ተርታ የተሰለፈችበትን የአየር ንብረትን በመቋቋም አረንጓዴ የኢኮኖሚ ልማት ስትራቴጂ ብትነድፍም፣ ለጥቂት ዓመታት በተግባር ላይ ሳታውለው ከቆየችበት ምክንያት አንዱ የፋይናንስ እጥረት ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ከከባቢ አየር ብክለት ነፃ የሆነና ዜሮ የካርቦንዳይኦክሳይድ በካይ ጋዝ ደረጃ ላይ ትደርስበታለች ተብሎ ይፋ የተደረገ ብሔራዊ ዕቅድ ነው፡፡
በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ በተደረገው የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ላይ ይፋ የተደረገው ይህ ስትራቴጂ፣ በወቅቱ እንግሊዝና ኖርዌይን ጨምሮ ጥቂት የአውሮፓ አገሮች ፖሊሲው ከሚፈልገው ገንዘብ ውስጥ ቁንጣሪውን ለመርዳት ቃል ገብተው ነበር፡፡ በፖሊሲው መሠረት ኢትዮጵያ ከካባቢ አየር ብክለት ነፃ የሆነ ኢኮኖሚ ለመፍጠር፣ 150 ቢሊዮን ዶላር ያላነሰ ገንዘብ ያስፈልጋታል፡፡
በወቅቱ ይፋ የተደረገው ስትራቴጂ እንደሚያትተው፣ ይህንን ገንዘብ ምዕራባውያኑ መስጠት ይጠበቅባቸዋል፡፡ የአካባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች ገንዘቡ ለአየር ብክለት ተጋላጭ የሆኑ (ለብክለት አስተዋጽኦ ሳይኖራቸው በግሪንሀውስ ጋዝ ልቀት የሚጎዱ) አገሮች በካሳ መልክ የሚያገኙት እንጂ ችሮታ ወይም ዕርዳታ ተደርጎ መታየት የለበትም ሲሉ ይሟገታሉ፡፡ 
መንግሥት 15 ዓመት ውስጥ ለአረንጓዴ ልማት ያስፈልገኛል ያለውን 150 ቢሊዮን ዶላር ፋይናንስ፣ ደኖችን በማፋፋት በእነሱም የሚታመቀውን ካርቦንዳይኦክሳይድ በመለካትና በመሸጥ የካርቦን ፋይናንስ እየተባለ የሚታወቀውን ስልት ለመከተል ያስባል፡፡ ከአሥራ አምስት ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ የነፍስ ወከፍ ገቢ በአማካይ 1000 ዶላር ደርሶ አገሪቱ መካከለኛ ኢኮኖሚ ይኖራታል ብሎ የሚያስበውና ለዚሁ እየሰራ ያለው የኢትዮጵያ መንግስት በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መሠረት ሊያሳካው እንደሚችል አቅዶ እየሰራ ይገኛል፡፡
ፖሊሲውን ለማስጸፈም ይረዳሉ የተባሉ የመተግበሪያ ረቂቅ ማኑዋሎች ላይ ውይይት ተደርጎባቸው ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ በዚህ መሠረት አዲስ የተቋቋመው የአካባቢና የደን ሚኒስቴር ስልታዊ የሆኑ የቴክኒክ ዝርዝር ማኑዋሎችን አዘጋጅቷል፡፡ መንግስት ከውጭ መንግሥታት ገንዘብ መገኘቱን ተከትሎ እያንዳንዱ የመንግሥት መሥሪያ ቤት፣ የሚያከናውነውን ሥራ በተመለከተ ዕቅዱን ሲያቀርብ፣ የሥራ ክንዋኔው የሚገመገምበት አሰራር ለውይይት ቀርቦ አስተያየት ተሰጥቶበታል፡፡
ዓለም የኢኮኖሚ ውጣውረድ ውስጥ መግባቷ ኢትዮጵያ የምትፈልገውን 150 ቢሊዮን ዶላር ገንዘብ ለማግኘት የሚያስችሉ አጋጣሚዎች ላይ ተፅዕኖ ቢኖረውም   አንዳንድ አገሮች የተሻለ የገንዘብ አስተዋጽኦ እያደረጉ ይገኛሉ። በሌላ በኩል ግን የአገሪቱን የአካባቢ ጥበቃ ሲመራ የነበረው ተቋም ማለትም የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ከዚህ ቀደም በነበረው የአሠራር ስልት ሲተች ቆይቷል፡፡
ይኸውም የተቋቋመለትን አካባቢን የመንከባከብ ተግባር በሥራ ጠባያቸው የጥቅም ግጭት ላለባቸው መሥሪያ ቤቶች ሥልጣኑን በውክልና መስጠቱ ነው፡፡ ለምሳሌ የመንገዶች ባለሥልጣን በሥሩ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ የሚያካሂድለት የራሱ አካል አለው፡፡ ግብርና ሚኒስቴር ዓላማው ግብርናን ማስፋፋት ሆኖ ሳለ፣ ደንን እንዲንከባከብ ኃላፊነት መውሰዱ የአገሪቱን የአካባቢ ጥበቃ በተቀናጀ ሁኔታ ለመፈጸም የራሱ አሉታዊና አወንታዊ ሁኔታዎች ሊኖሩት እንደሚችሉ መገመት አይከብድም።
እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ በአለማችን ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ ከሆኑ 10 ሀገራት መካካል አንዷ መሆኗን የመንግስታቱ ድርጅት የአካባቢ ጥበቃ ድርጅት ጥናት ያመለክታል፡፡ በአማካይ ሙቀት መጠን መጨመርና የዝናብ ስርጭት መዛባት የመሰሉ ቀጥተኛ የሆኑ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች ተጠቂ ናት፡፡ የአገሪቱ 80 በመቶ ዜጎች መተዳደሪያ እንዲሁም 40 በመቶ ሀገራዊ ምርት የተመሰረተበት የግብርናው ዘርፍ፤ የአየር ንብረት ለውጡ ቀጥተኛ ተጠቂ መሆናቸው ተጋለጭነቱን ያባብሰዋል፡፡ የአየር ንብረት በአለማችን ላይ ከደቀነው ተጨባጭ አደጋ ባሻገር የዘላቂ ልማት አማራጮችን ይዞ መምጣቱ አልቀረም፡፡
መንግስት በዘርፉ የተሻለ ልምድ ያላቸውን የልማት አጋር አካላትን ለመሳብ ጥረት እንደሚደረግም ስትራቴጂው ያመለክታል፡፡ ኢትዮጵያ በተለመደው የኢኮኖሚ ዕድገት አማራጭ ብትጓዝ 2002 . የነበራት 150 ሚልዮን ቶን የሙቀት አማቂ ጋዞች ልቀት 2022 . ከዕጥፍ በላይ በማደግ 400 ሚልዮን ቶን ይደርሳል፡፡
የልማቱ ኢትዮጵያ የምትከተለው የአረንጓዴ ልማት ዕድገት አማራጭ ምንነት፣ ከልማትና ትራንስፎርማሽን ዕቅዱ ጋር ያለው ቁርኝት፣ አዋጭነት፣ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብና ለአከባቢያዊ ሀገራት ያለው ፋይዳ እንዲሁም ተግዳሮቱን በተገቢው መንገድ በመዳሰስ  የአረንጓዴ ልማት ዕቀድ የአየር ንብረት ለውጥ ታሪካዊ ሀላፊነት ያለባቸው የበለጸጉት ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ የሚያመጣውን ተጽኖ ለመቀነስ የታዳጊ አገራት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት እየተሰራ እንዳል መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
ከታዳሽ ሀይል በተለይም ከውሃ ሀይልን በማመንጨት በተነጻጻሪ ከሌሎች ሀገራት ቀድማ አረንጓዴ ልማትን መተግበር የጀመረችው ኢትዮጵያ፣ ሀገሪቱ ለአየር ንብረት ለውጥ ያላትን ተጋላጭነት በፍጥነት የአረንጓዴ ልማት ማስፈጽሚያ ስትራቴጂ ቀርጻለች፡፡ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመን፣ የደን ልማት፣ ታዳሽ ሀይል አማራጭ መከተል እንዲሁም የትራንስፖርት፣ የኢንዱስትሪ የቤት ልማትን በተስማሚ ቴክኖሎጂ መተግበር የአገሪቱ የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂው መሰረቶች ናቸው፡፡
የስትራቴጂው መሰረቶች አተገባበር እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡ የመጀመሪያው የስትራቴጂው መሰረት የግብርናውን ዘርፍ ማዘመን ሲሆን፣ ዘርፉ የአገሪቱ ኢኮኖሚ መሪና የአብዛኛው የሀገሪቱ ዜጎች መተዳደሪያ መሆኑ ልዮ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጎታል፡፡ የግብረናውን ዘርፍ ለማሳደግ ከዚህ ቀደም በተለምዶ እንደሚደረገው የሚታረስ መሬትን ማስፋፋትና የቀንድ ከብቶችን ቁጥር ከማሳደግ ይልቅ የመሬትንና የቀንድ ከብቶችን ምርታማነት ማሳደግ የአረንጓዴ ልማት አቅጣጫ ነው፡፡
የተሻሻሉ የሰብልና የቀንድ ከብት ዝርያዎችን አርሶ አደሩ እንዲጠቀም ማድረግ የግብርና ዘርፍ ማሳደጊያ ሰልት ነው፡፡ የደን ጭፍጨፋን ለመቀነስ በተለይም በተራቆቱና በተጎዱ አከባቢዎች ዝቅተኛ፣ መካከለኛ እንዲሁም ከፍተኛ የመስኖ ልማት ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋትም በስትራቴጂው የተያዘ ዕቅድ ነው፡፡
በሁለተኛ ደረጃ የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂው የተመሰረተው የደን ሃብት ልማት ላይ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ደን 80 በመቶ ለሚሆኑ በተለይም በገጠሩ የሀገሪቱ ክፍል ለሚኖሩ ዜጎች የሀይል ምንጭ ነው፡፡ ከዚህ ንብ በማነብ፣ የጫካ ቡና እና ከጣውላ የሚገኘው ምርት የጠቅላላ ሀገራዊ ምርትን 4 በመቶ ድርሻ ይዛል፡፡
ለአገሪቱ ጤናማ ዕድገት ከፍተኛ ሚና ያለው የደኑ ዘርፍ ጉዳት ለመቀነስ የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ ስልቶችን ቀይሷል፡፡ ዜጎች ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችን እንዲጠቀሙ ማድረግ፤ ከማገዶ ውጭ  በኤሌክትሪክ፣ ባዮጋዝና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ምድጃዎች ህብረተሰቡ እንዲጠቀም በማድረግ የደን ምንጠራን ትርጉም ባለው መጠን መከላከል የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂው ሌላው ስልት ነው፡፡
ከዚህ ጎን ለጎን የተጎዱ መሬቶችን በመከለል እንዲያገግሙ ማድረግና ተጨማሪ መሬትን በደን በመሸፈን የደን ልማቱ እንዲስፋፋ የሚያደርጉ ስልቶች ናቸው፡፡ ኤሌክትሪክ ለዘመናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ የሀይል ምንጭ ነው፤ ይህንኑ ተታሳቢ በማድረግ፣ ለአገር ውስጥና ለአከባቢያዊ ፍጆታ የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ሀይል ፍጆታን፤ ከታዳሽ የሀይል ምንጮች ማስፋፋት የስትራቴጂው ሶስተኛ መሰረት ነው፡፡
ከከተሞችና እንዱስትሪዎች የሀይል ፍጆታ አንስቶ ለመስኖ የሚያስፈልገውን ውሃ ለመግፋት ይዉላል፡፡ በአማካይ 10 በመቶ በላይ የሚያድገው የሀገሪቱ አኮኖሚ በአመት 14 በመቶ በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ያስፈልጓል፡፡ ኢትዮጵያ ከራሷ አልፎ ለሎች የሚተርፍ ዕምቅ ታዳሽ ሀይል አማራጭ እንዳላት በዘርፉ የተሰሩ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ ኢትዮጵያ ከታዳሽ የሀይል ምንጮች ብቻ 60 ሺህ ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚያስችል ዕምቅ አቅም አላት፡፡
ከዚህም ውስጥ የሀይድሮ ዘርፉ 45 ሺህ ሜጋ ዋት በመያዝ፣ የታዳሽ ሀይል ምንጭ 75 በመቶ ድርሻ ይዟል፡፡ ከጂኦተርማል፣ ከንፋስና ከፀሀይ የሚገኘው ቀሪውን 25 በመቶ ድርሻ ይይዛል፡፡ ኢትዮጵያ ያላትን ታዳሽ የሀይል አማራጭ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የተረፈውን ደግሞ ወደ ውጭ በመላክ 50 ሚልዮን ቶን ለአየር ንብረት ዋነኛ መንስዔ የሆኑት ሙቀት አማቂ ጋዞችን መቀነስ ትችላለች፡፡

No comments:

Post a Comment